Ethiopian Freight Forwarders and Shipping Agents Association

FBC – ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የሎጂስቲክ ፓስፖርት ተቋም አባል ሆነች

Article:

ኢትዮጵያ የዓለም አቀፉ የሎጂስቲክ ፓስፖርት ተቋም አባል ሆነች

Snippet:

አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 11 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ)በኢትዮጵያ የዕቃዎች አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማኅበር አማካኝነት ኢትዮጵያ ዓለም አቀፉን የሎጂስቲክ ፓስፖርት ተቋም አባል ሆናለች።

ዓለምአቀፉ የሎጂስቲክ ፓስፖርት ባለፈው የፈረንጆቹ ዓመት በስዊዘርላንድ ዳቮስ ከተማ በተካሄደው የዓለም ኢኮኖሚ ፎረም ላይ የተመሠረተ ተቋም ነው።

ተቋሙ ዓለም አቀፍ ብሔራዊ የንግድ ተቋማትን ከሎጂስቲክ የአሠራር ሥርዓት ጋር ለማስተሳሰር እንዲሁም ለታዳጊ ገበያዎች የተለያዩ ዕድሎችን ለመፍጠር እየሰራ ይገኛል።

ዱባይን ዋነኛ የመገናኛ ማዕከል በማድረግም አፍሪካ፣ እስያና ላቲን አሜሪካን በማገናኘት ቀልጣፋ የሎጂስቲክ መረብ ለመፍጠር ትኩረት ማድረጓን ኢዜአ ዘግቧል።

የኢትዮጵያ የዕቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማኅበር ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ዳዊት ውብሸት፥ ኢትዮጵያ በማኅበሩ በኩል የተቋሙ አባል ሆናለች ብለዋል።

Link:

https://www.fanabc.com/ኢትዮጵያ-የዓለም-አቀፉ-የሎጂስቲክ-ፓስፖ/

Share on

Facebook
Twitter
LinkedIn
Telegram
WhatsApp
Email

More Updates